ይህ ዝቅተኛ ዳታን በመጠቀም ጽሑፍ ብቻ የሚቀርብበት የቢቢሲ አማርኛ ድረ ገጽ ነው
ትራምፕ ያለ ምክር ቤት ፈቃድ ኢራን ላይ ወታደራዊ እርምጃ መፈጸም እንዳይቀጥሉ ተወሰነ
ሪፐብሊካኖች በአብላጫ የያዙት የአሜሪካ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት፤ ትራምፕ የኢራንን ጦርነት እንዲያቆሙ የቀረበውን የውሳኔ ሐሳብ አጸደቀ።
ትራምፕ ያለ ምክር ቤት ፈቃድ ወታደራዊ እርምጃ መውሰድ እንዳይቀጥሉም ውሳኔ ተላልፏል።
ብዙ ሪፐብሊካን እንደራሴዎች ከዴሞክራቶች ጎን በመቆማቸው ውሳኔው 50 ለ48 በሆነ አብላጫ ድምጽ ጸድቋል።
በሰኔ ወር መባቻ ላይ የአሜሪካ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ትራምፕ በኢራን ላይ ተጨማሪ ጥቃት እንዳይፈጽሙ የሚያግድ ውሳኔ ማሳለፉ ይታወሳል።
ውሳኔውን ያሳለፉት 215 ለ 208 በሆነ ድምጽ ሲሆን፤ አራት ሪፐብሊካኖች ጦርነቱን በመቃወም ዲሞክራቶችን ተቀላቅለዋል።
በወቅቱ የዋይት ሐውስ ባለሥልጣን በበኩላቸው የተኩስ አቁም ላይ በመደረሱ የአሜሪካ ወታደሮች እንደሚወጡ ለቢቢሲ ገልጸዋል።
ውሳኔው የጸደቀው ሁለት ሪፐብሊካን እንደራሴዎች በምክር ቤቱ ስላልነበሩ እንደሆነም አክለዋል።
የምክር ቤቱ ውሳኔ ተምሳሌታዊ ሲሆን፤ በሁለቱም ኮንግረሶች ቢጸድቅም እንኳን ለትራምፕ ተልኮ እንደ ሕግ አይተገበርም።
ትራምፕ ከኢራን ጋር ጦርነት ለማቆም ዕቅድ ቢያወጡም ሪፐብሊካኖች አሁንም ጥያቄ ማንሳታቸውን ቀጥለዋል።
በአውሮፓውያኑ 1973 'ዋር ፓወርስ' የተባለው ውሳኔ ከተላለፈ ወዲህ ሁለቱም ምክር ቤቶች የፕሬዝዳንትን ወታደራዊ እርምጃ የመውሰድ አቅም ለመገደብ ሲወስኑ የአሁኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው።
ውሳኔው በፕሬዝዳንቱ ፊርማ ሕግ ሆኖ የሚተገበር ሳይሆን የምክር ቤቶቹን ስሜት የሚያንጸባርቅ ነው።
በአውሮፓውያኑ 2019 ሁለቱ ምክር ቤቶች ያሳለፉትን ከኢራን የእርስ በርስ ጦርነት ወታደሮችን የማስወጣት የውሳኔ ሐሳብ፤ ትራምፕ ድምጽን በድምጽ የመሻር ሥልጣናቸውን በመጠቀም ውድቅ አድርገዋል።
የመካከለኛው ምሥራቅ ተንታኝ ላውራ ብሉምፊልድ "ውሳኔው እጅን ከማሰር ይልቅ የመግረፍ ያህል ነው። ሕጋዊ አሳሪነት የለውም" ብለዋል።
ሆኖም ግን የአሜሪካውያንን ስሜት የሚያሳይ መሆኑን አስረድተዋል።
የውሳኔ ሐሳቡ መጽደቁ ዋይት ሐውስ የኢራንን ጦርነት ለማቆም መንገድ እንዲፈልግ ጫና ያሳድራል።
በጦርነቱ ምክንያት የኑሮ ውድነት በመከሰቱ አሜሪካውያን ቁጣቸውን ገልጸዋል።
አሁን ላይ የውሳኔ ሐሳቡ መጽደቁ ትራምፕ ከሪፐብሊካኖች የገጠማቸውን ተቃውሞ ያሳያል።
አንዳንድ ሪፐብሊካኖች ትራምፕን መቃወማቸውን የሚያሳዩ የምክር ቤት ውሳኔዎች እያሰለፉ ነው።
በቀደመው አስተዳደር "ዒላማ ተደርገናል" ላሉ ሰዎች ካሳ ለመስጠት 1.8 ቢሊዮን ዶላር እንዲመደብ ትራምፕ ያቀረቡት ሐሳብ በቅርቡ ውድቅ መደረጉ ይታወሳል።
የኢራን ጦርነት ከተጀመረ ወዲህ የሕግ መወሰኛው ምክር ቤት የፕሬዝዳንቱን ጦርነትን የተመለከተ ሥልጣን ለመገደብ ድምጽ ሲሰጥ የአሁኑ ለ10ኛ ጊዜ ነው።
ውሳኔው በተላለፈበት ቀን ፔንታገን ምክር ቤቱ 80 ቢሊዮን ዶላር እንዲፈቅድ ጠይቋል። ከዚህ ገንዘብ አብዛኛው በኢራን ጦርነት የሚውል ይሆናል።
ከ60 ቀናት በላይ ወታደራዊ እርምጃ ለመቀጠል የኮንግረስ ይሁንታ እንደሚያስፈልግ የፌደራል ሕግ ይደነግጋል።
የፕሬዝዳንት ትራምፕ ጽህፈት ቤት ብሔራዊ ደኅንነት አደጋ ውስጥ መውደቁን በመግለጽ 30 ቀናት መጨመር ይችላል።
በአሜሪካ እና ኢራን የመግባቢያ ሰነድ መሠረት፤ ኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብሯን በተመለከተ ስምምነት ላይ ለመድረስ 60 ቀናት ተሰጥቷታል።