በቬንዙዌላ የመሬት መንቀጥቀጥ የሞቱ ሰዎች ቁጥር በእጥፍ መጨመሩ ተገለጸ

የፎቶው ባለመብት, Getty Images
በቬንዙዌላ በደረሰው የመሬት መንቀጥቀጥ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 589 መድረሱን እና 2,980 ሰዎች መጎዳታቸውን የአገሪቱ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዴልሲ ሮዴሪጌዝ አስታወቁ።
በፍርስራሾች ውስጥ ያሉ ሰዎችን ለማውጣት የሚደረገው ጥረት በቀጠለበት በአሁኑ ጊዜ ከተለያዩ አገራት እርዳታ ወደ ቬንዙዌላ እየገባ ነው።
አሜሪካ ትናንት ሐሙስ ከፍተኛ መጠን ያለው እርዳታ ወደ አገሪቱ መላኳን ስታሳውቅ።ከስዊትዘርላንድ የተላኩ ሰማንያ የነፍስ አድን ሠራተኞች እና 18 ቶን ቁሳቁሶች ቬንዙዌላ መድረሳቸውን የአገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘገበ።
የቬንዙዌላ ቴሌቪዥን እንደዘገበው ከሆነ፣ ቡድኑ ዓርብ ማለዳ ላይ የደረሰ ሲሆን፣ ስምንት አነፍናፊ ውሻዎችም የተካተቱበት ነው።
አክሎም፣ ከመሬት መንቀጥቀጡ ክስተት በኋላ የአስቸኳይ ጊዜ ምላሽ በመስጠት ስዊትዘርላንድ ከመጀመሪያዎቹ አገራት መካከል መሆኗን ገልጿል።
ከሜክሲኮም እንዲሁ ቁሳቁሶችን የያዙ የነፍስ አድን ሠራተኞች ወደ አገሪቱ መድረሳቸውን የቬንዙዌላ ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት ዴልሲ ሮድሪጌዝ ገልጸዋል።
የዩናይትድ ስቴትስ ደቡባዊ ዕዝ ደግሞ አንድ ከፍተኛ ወታደራዊ ባለሥልጣኑ የዕዙን የድጋፍ ጥረት ለመከታተል መድረሳቸውን አስታውቋል።




















