የዓለም ዋንጫ አሸናፊዎች ብዙም ያልተሰሙ እውነታዎች

ታትሟል
የንባብ ጊዜ: 4 ደቂቃ

የዓለም ዋንጫን ማን ያሸንፋል ለሚለው ጥያቄ መልሱን ማግኘት ቀላል አይሆንም። በኮምፒውተር በመታገዝም ጥረቶች ቀጥለዋል።

ግምት በማስቀመጥ ታዋቂው የጀርመን የፋይናንስ ተንታኝ ዮአኪም ክሌመንት ድንቅ ብቃት ካላቸው ቡድኖች መካከል አሸናፊው በዕድል የሚለይ ይሆናል ይላል።

የተጫዋቾች አቋም፣ የዳኞች ውሳኔ እና ዕድል አሸናፊውን ይለያሉ። እናም ከአሁኑ ለመገመት አዳጋች እንደሚሆን ተንታኙ ይናገራል።

ከዚህ ቀደም በነበረው ልምድ አሸናፊዎችን ለመለየት የተለያዩ መንገዶች ጥቅም ላይ ውለዋል።

84 አገራት በዓለም ዋንጫ ቢሳተፉም ማሸነፍ የቻሉት አርጀንቲና፣ ብራዚል፣ እንግሊዝ፣ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ ጣሊያን፣ ስፔን እና ኡራጓይ ናቸው።

ጀርመን ስምንት ጊዜ ለዋንጫ ፍልሚያ አልፋለች። ብራዚል ሰባት ጊዜ፣ አርጀንቲና እና ጣሊያን ደግሞ ስድስት ጊዜ አልፈዋል።

ስፔን በአውሮፓውያኑ 2010 በማሸነፍ የባለ ድሎችን ጎራ ተቀላቅላለች።

ሦስት ጊዜ ለዋንጫ ተጫውታ አንዴም ያላሸነፈችው ደግሞ ኔዘርላንድስ ናት።

አገራት ከአፍሪካ እና ከእስያ ለዓለም ዋንጫ ያለፉት በሁለት አጋጣሚዎች ብቻ ነው። ደቡብ ኮሪያ በ2002 እና ሞሮኮ በ2022።

የአካባቢ ሁኔታ

በአውሮፓውያኑ 1930 በኡራጓይ የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫ ተከናወነ። የመጨረሻውን የዓለም ዋንጫ በ2022 ያዘጋጀችው ኳታር ናት።

ከአህጉሩ ውጭ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ የሆነ አገር ማግኘት ከባድ ቢሆንም ስድስት ጊዜ እውን ሆኗል።

ከ22 ጨዋታዎች መካከል ስድስት ጊዜ ከአህጉር ውጭ ድል የተገኘው በብራዚል (በ1958፣ 1994፣ 2002)፣ በስፔን (በ2010)፣ በጀርመን (በ2014) እና በአርጀንቲና (በ2022) ነው።

ከደቡብ አሜሪካ እና አውሮፓ ውጭ በሁለት ቀጣናዎች የዓለም ዋንጫ ተከናውኗል።

ብሔራዊ ቡድኖች አህጉራቸው ላይ ሲሆኑ የተሻለ ውጤታማ ይሆናሉ። በጉዞ አለመድከማቸው እና በደጋፊዎች መከበባቸው ዋነኛ ምክንያቶች ናቸው።

ስድስት ጊዜ የዓለም ዋንጫ አዘጋጅ አገራት አሸናፊ ሆነዋል።

በ2014 በብራዚል ዓለም ዋንጫ ሰባት የላቲን አሜሪካ አገራት አልፈዋል። ከአውሮፓ ስድስት አገራት ከምድባቸው አልፈዋል።

ብዙውን ጊዜ የአውሮፓ አገራት ከሌሎች አህጉራት በበለጠ ለዓለም ዋንጫ ይደርሳሉ።

ከብራዚል የዓለም ዋንጫ በኋላ በሩሲያ 10 የአውሮፓ አገራት ማለፍ ችለዋል። ከላቲን አሜሪካ ግን አምስት አገራት ብቻ አልፈዋል። ለግማሽ ፍጻሜ ከደረሱት አራቱ የአውሮፓ አገራት ነበሩ።

የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ አዳዲስ ክብረ ወሰኖች ይመዘገቡበታል።

በሦስት አገራት የሚዘጋጅ የመጀመሪያው የዓለም ዋንጫ ነው። እንደ ከዚህ ቀደሙ 32 ሳይሆን 48 አገራት ያሳትፋል።

ኪዩራሶው፣ ኬፕ ቬርዲ፣ ዮርዳኖስ እና ኡዝቤኪስታን ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም ዋንጫ ይሳተፋሉ።

የፊፋ ድልድል

በቅርብ ጊዜ ውስጥ ጥሩ ብቃት ያሳዩ ቡድኖች በዓለም ዋንጫ ተጠባቂ ይሆናሉ። ይሄ ብቻውን ግን አሸናፊውን ለመገመት አያስችልም።

ፊፋ በአውሮፓውያኑ 1992 ያወጣው የደረጃ ምድብ ለአንድ ቡድን ባደላ መንገድ ግጥሚያዎች እንዳይደለደሉ ይረዳል።

ፊፋ እውቅና የሰጣቸው ግጥሚያዎች ውጤት እንደ መመዘኛ ጥቅም ላይ ይውላል። ይህም የወዳጅነት ጨዋታዎች እና ከእግር ኳስ ውጭ ያሉ ስፖርቶች ውጤቶችን ይጨምራል።

የዓለም ዋንጫ አሸናፊ የሚሆነው የበላይነት ካላቸው ከ10 እስከ 15 ከሚደርሱ ቡድኖች አንደኛው ይሆናል።

አሁን በፊፋ የደረጃ ምድብ ከላይ የተቀመጠችው አርጀንቲና ናት። ይህ ድልድል የዓለም ዋንጫ የሚጀመርበት ቀን ይለወጣል። ምክንያቱም አገራት ግጥሚያዎች በማድረግ ውጤት ማስመዝገብ ይጀምራሉ።

ኃያላን ሲረቱ

እንደ ብራዚል፣ ጀርመን፣ ጣሊያን እና አርጀንቲና ያሉ የዓለም ዋንጫ ባለ ድል ቡድኖች ሁሌም አይሳካላቸውም።

በዓለም ዋንጫ ታሪክ ሁለት ጊዜ በተከታታይ ማሸነፍ የቻሉት ጣሊያን (በ1934 እና 1938) እና ብራዚል (1958 እና 1962) ናቸው።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በዓለም ዋንጫ ኃላያላን አገራት ብዙም ድል እየቀናቸው አይደለም።

ከብራዚል (የ2002 አሸናፊ) እና ፈረንሳይ (የ2018 አሸናፊ) በስተቀር ከ2002 ወዲህ ከስድስት የዓለም ዋንጫ አሸናፊ አገራት አራቱ ከምድባቸው ማለፍ አልቻሉም።

የውጭ አገር አሠልጣኞች

በዓለም ዋንጫ የውጭ አገር አሠልጣኞች መቅጠር የተለመደ ነው። ባለፉት ሦስት አስርት ዓመታት የውጭ አሠልጣኞችን የመቅጠር ነገር በጉልህ የሚታይ ሆኗል።

ከዚህ ቀደም ከተሳተፉ የውጭ አገራት አሠልጣኞች የ2026 ከፍተኛው ነው። ከ48 አሠልጣኞች 27ቱ የውጭ አገር ናቸው።

ብራዚልን የሚያሠለጥኑት ጣልያናዊው ካርሎ አንቼሎቲ ሲሆኑ፣ የእንግሊዝ አሠልጣኝ ጀርመናዊው ቶማስ ቱቻል ናቸው።

ከዚህ ቀደም የውጭ አገር አሠልጣኝ ይዞ የገባ የትኛውም አገር አላሸነፈም።

ከአውሮፓውያኑ 1982 ወዲህ (ከ1986 እና 2010 በስተቀር) ባለፉት 11 የዓለም ዋንጫ ግጥሚያዎች ለዋንጫ ፍልሚያ ከደረሱት አገራት ቢያንስ አንደኛቸው የባየር ሙኒክ ወይም ኢንተር ሚላን ተጫዋች ነበራቸው።

በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ ከ48 ብሔራዊ ቡድኖች በ15 ውስጥ የባየር ሙኒክ እና ኢንተር ሚላን ወይም የሁለቱም ክለቦች ተጫዋቾች እንደሚገኙበት ፊፋ አስታውቋል።