በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም ተባለ

የፎቶው ባለመብት, AFP via Getty Images
አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል የሚተላለፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም እንደማይጠበቅባቸው የአሜሪካው ምክትል ፕሬዝዳንት ጄዲ ቫንስ ገለጹ።
ምክትል ፕሬዝዳንቱ ከሲኤንቢሲ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃል ምልልስ “የሆርሙዝ ወሽመጥ ለረዥም ጊዜ ከክፍያ ነጻ ይሆናል ብለን እንጠብቃለን” ብለዋል።
ጦርነቱ መነሳቱን ተከትሎ ኢራን በሆርሙዝ ወሽመጥ ለሚያልፉ መርከቦች የክፍያ ሥርዓት ዘርግታ ቆይታለች።
አሁን ከአሜሪካ ጋር በተደረሰው ስምምነት አማካኝነት በሆርሙዝ ወሽመጥ በኩል ያለ ክፍያ ማለፍ ጊዜያዊ ሊሆን እንደሚችል የተናገሩት ጄዲ ቫንስ፤ ዘላቂ መፍትሔ ለማግኘት ከኢራን ጋር መወያየት እንደሚቀጥሉ አስረድተዋል።
ክፍያውን ማስቀረት “በቴክኒክ ድርድሩ ወቅት የምናነሳው ጉዳይ ይሆናል። አብረን በጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጠን የምንወያይባቸው በጣም ጠቃሚ ነጥቦች ይኖራሉ” ብለዋል።












