ቀጥታ, በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ ለመወያየት ኦማን ያዘጋጀችው የባሕረሰላጤው አገራት ጉባዔ ወደ ሌላ ጊዜ ተላለፈ

ኦማን በሆርሙዝ ወሽመጥ አዲስ የመርከቦች መተላለፊያ ላይ ለመነጋገር ለሰኞ አቅዳ የነበረውን ቀጣናዊ ጉባዔ መሰረዟን አስታወቀች። ጉባዔው ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው በአገሪቱ ደቡባዊ ከተማ ሳላህ ነበር። የኦማን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እሁድ አመሻሽ ላይ ባወጣው መግለጫ ጉባዔው ወደ ሌላ ቀን የተላለፈው “ገንቢ የሆነ ውይይት እንዲካሄድ የሚያስችል ሁኔታን ለመፍጠር ነው” ብሏል።

ጭምቅ ሃሳብ

የቀጥታ ሽፋን

  1. በኢንዶኔዥያ መርከብ ተገልብጦ ስድስት ሰዎች ሲሞቱ 130 የሚሆኑት ደብዛቸው ጠፋ

    የተገለበጠችው መርከብ

    የፎቶው ባለመብት, ndonesian Navy

    የምስሉ መግለጫ, በፍለጋው እና ነፍስ አድን ጥረት ላይ የተሰማራው የኢንዶኔዥያ ጦር የተገለበጠውን ጀልባ ምሥል አስቀርቷል

    በኢንዶኔዥያ ጃቫ ባሕር ላይ አንድ አነስተኛ መርከብ ተገልብጦ ስድስት ሰዎች ሲሞቱ 130 የሚሆኑት ደብዛቸው መጥፋቱን ባለሥልጣናት አስታወቁ።

    እስካሁን ሌሎች 107 ሰዎችን መታደግ ተችሏል።

    መርከቡ ቅዳሜ ዕለት ከሱራባያ ወደ ደቡባዊ ካሊማንታን ከተማ ባንጃርማሲን እየተጓዘ ሳለ ነበር አደጋው የደረሰው።

    በአደጋው ሥፍራ መርከቦች እና ሄሊኮፕተር የተሰማሩ ሲሆን 280 የነፍስ አድን ሠራተኞች የሕይወት አድን ጥረት እያደረጉ ነው።

    በአካባቢው ያለው መጥፎ የአየር ሁኔታ የጠፉ ሰዎችን የመፈለግ ጥረቱን አዳጋች እንዳደረገው ተገልጿል።

    በጃቫ ባሕር ላይ ያሉ ሁሉም ጀልባዎች የሆነ አጠራጣሪ ምልክት ካዩ እንዲያሳውቁ ተነግሯቸዋል።

    መርከቡ 213 መንገደኞችን እና 30 ሠራተኞችን አሳፍሮ እንደነበር ተነግሯል።

    እንደ የባሕር ትራንስፖርት ተቆጣጣሪዎች ከሆነ መርከቡ ከሱርባያ የተነሳው ቅዳሜ ጠዋት 4፡33 ሰዓት ላይ ሲሆን በባንጃርማሲን እሁድ 8፡00 ሰዓት ላይ ይደርሳል ተብሎ ይጠበቅ ነበር።

    በኢንዶኔዥያ ከ17 ሺህ በላይ ደሴቶች ያሉ ሲሆን መርከቦች የተለመዱ የመጓጓዣ መንገዶች ናቸው።

    የባሕር ትራንስፖርት አደጋም ያልተለመደ አይደለም። የመንግሥት መረጃ እንደሚያሳየው ከአውሮፓውያኑ 2020 እስከ 2026 ባሉት ዓመታት 111 የመርከብ አደጋዎች አጋጥመዋል።

    ሐምሌ ወር ላይ በምዕራባዊ ፖላሲ ደሴት አንድ መርከብ ሰጥማ 58 ሰዎች ከአደጋው ሲተርፉ፣ ሦስት ሰዎች ሞተዋል፤ ሌሎች 14 ሰዎች ደግሞ እስካሁን የገቡበት አልታወቀም።

    ባለፈው ወርም አንድ መርከብ በማዱራ ደሴት በእሳት ተያይዞ አምስት ሰዎች መሞታቸው ይታወሳል።

    የተጎጂ ቤተሰቦች ሲያለቅሱ

    የፎቶው ባለመብት, Donny Muslim / BBC

  2. በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ ለመወያየት ኦማን ያዘጋጀችው የባሕረ ሰላጤው አገራት ጉባዔ ወደ ሌላ ጊዜ ተላለፈ

    የሆርሙዝ ወሽመጥ

    የፎቶው ባለመብት, Reuters

    ኦማን በሆርሙዝ ወሽመጥ አዲስ የመርከቦች መተላለፊያ ላይ ለመነጋገር ለሰኞ አቅዳ የነበረውን ቀጣናዊ ጉባዔ መሰረዟን አስታወቀች።

    ጉባዔው ሊካሄድ ታቅዶ የነበረው በአገሪቱ ደቡባዊ ከተማ ሳላህ ነበር።

    የኦማን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እሁድ አመሻሽ ላይ ባወጣው መግለጫ ጉባዔው ወደ ሌላ ቀን የተላለፈው “ገንቢ የሆነ ውይይት እንዲካሄድ የሚያስችል ሁኔታን ለመፍጠር ነው” ብሏል።

    መግለጫው አክሎም ስብሰባውን ለሌላ ጊዜ ማስተላለፍ ያስፈለገው ለቀጣናው ደህንነትና መረጋጋት አስተዋጽኦ የሚያደርጉ እንዲሁም የቀጣናውን ሕዝቦች የትብብርና የሰላም ፍላጎት የሚያሟሉ ዘላቂ መግባባቶች ላይ ለመድረስ የሚያስችሉ የውይይት ሁኔታዎችን ለመፍጠር ካለ ፍላጎት በመነሳት መሆኑ ተገልጿል።

    የኦማን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ባድር አልቡሳይዲ “መግባባት ላይ ለመድረስ ካለ ፍላጎት በመነሳት ጉባዔው ነገ [ሰኞ] በሳላህ ለማካሄድ ታቅዶ የነበረው ጉባዔ ወደ ሌላ ጊዜ ተላልፏል” ሲሉ በኤክስ ገጻቸው ላይ አጋርተዋል።

    “መረጋጋት እና በቀጣናውን ዘላቂ ትብብር የሚያመጣ ውይይት ለማካሄድ ቁርጠኞች ነን” ሲሉም በመግለጫቸው ላይ አስታውቀዋል።

    አልቡሳይዲ በኤክስ ገጻቸው ላይ በለጠፉት መግለጫ ላይ በጉባዔው ላይ ይሳተፋሉ ተብሎ የሚጠበቀውን የባህሬን፣ ኢራን፣ ኢራቅ፣ ዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ፣ ኦማን፣ ኳታር፣ ሳዑዲ አረቢያ እና ኩዌት ባንዲራዎችን አጋርተዋል።

    ጉባዔው የሚካሄድበትን አዲሱን ቀን ያላስታወቁት የኦማኑ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለምን ወደ ሌላ ጊዜ እንደተላለፈም የሚገልጽ ማብራሪያ አልሰጡም።

    ጉባዔው ወደ ሌላ ጊዜ የተላለፈው ባህሬን የቀጣናው ሚኒስትሮች ጉባዔ ላይ ኢራን በመካተቷ የተነሳ እንደማትሳተፍ ካስታወቀች በኋላ ነው።

    የባህሬን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቅዳሜ ዕለት ከኢራን ጋር ያለን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሳይሻሻል አገሪቱ በምትሳተፍበት የትኛውም የሚኒስትሮች ጉባዔ ላይ አንገኝም ሲሉ አስታውቀዋል።

    የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ኢስማኤል ባጋይ አርብ ዕለት ስምንት የባሕረ ሰላጤው አገራት ሚኒስትሮች የሚገኙበትን እና ኦማን የምታስተናግደውን ጉባኤ ቴህራን ማቀናጀቷን ተናግረው ነበር።

    የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ፣ እሁድ ዕለት በለንደን ለሚገኘውና በአረብኛ ቋንቋ ለሚሰራጨው 'አል-አራቢ አል-ጃዲድ' የተባለ የዜናአውታር እንደተናገሩት፣ "የዚህ ስብሰባ ዋናው እና ብቸኛው አጀንዳ በሆርሙዝ ባህር ወሽመጥ ውስጥ የሚገኘው አዲሱ የባህር መስመር ነው" ብለዋል።

    ሚኒስትሩ አክለውም ኢራን እና ኦማን አዲሱን መስመር የሚወስን ስምምነት እንዲሁም ዝግጅቶቹን በዝርዝር የሚያሳዩ ካርታዎችን እና የጋራ መግለጫን አጠናቀዋል ብለዋል።

    ከኦማን ጋር የተደረገው ስምምነት የሆርሙዝ ባህር ወሽመጥ እንደገና መከፈትን “በምንም መልኩ” እንደማያመለክት አጽንኦት ሰጥተዋል።

    በኢራን ጦርነት በተደጋጋሚ ጥቃት ከደረሰባቸው አገራት መካከል ባህሬን አንዷ ናት።