
የፎቶው ባለመብት, etv
የምስሉ መግለጫ, የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሜላት ወርቅ ኃይሉበአማራ እና በኦሮሚያ የተወሰኑ አካባቢዎች ድምጽ መስጠት ከተጀመረ በኋላ በተፈጠረ የፀጥታ ችግር ምክንያት የድምጽ አሰጣጥ ሂደቱ
መቋረጡን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ።
የምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ሜላት ወርቅ ኃይሉ ዛሬ ከማለዳው12
ሰዓት ጀምሮ እየተካሄደ ያለውን ሰባተኛው አጠቃላይ ምርጫን አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ በመላው አገሪቱ ካሉ የምርጫ ጣቢያዎች 50,188ቱ በሰዓቱ 12 ሰዓት ላይ ድምጽ አሰጣጥ መጀመሩን ተናግረዋል።
ነገር ግን 695 የምርጫ ጣቢያዎች በሰዓቱ አለመከፈታቸውን የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢዋ ገልጸው፤ እነዚህ ምርጫ ጣቢያዎች በ30
ደቂቃ እና በአንድ ሰዓት ዘግይተው መከፈታቸውን አብራርተዋል።
በፀጥታ ምክንያት ያልተከፈቱ 143 የምርጫ ጣቢያዎች መኖራቸውን የተናገሩት ሰብሳቢዋ፣ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ውስጥም የድምጽ
አሰጣጥ ሂደቱ ከተጀመረ በኋላ በተፈጠረ የፀጥታ ችግር የተቋረጠባቸው ቦታዎች እንዳሉ በመግለጫቸው ላይ አመልክተዋል።
የምርጫ ቦርድ ቀደም ሲል ከትግራይ ክልል በተጨማሪ በስምንት የምርጫ ክልሎች ምርጫ እንደማይካሄድባቸው አስታውቆ ነበር።
የቦርዱ ሰብሳቢ በፀጥታ ችግር ምክንያት ምርጫ መካሄድ ባልተቻለባቸው የአማራ እና የኦሮሚያ ክልሎች ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች ምርጫው እንዳይካሄድ የትራንስፖርት እንቅስቃሴ ማገዳቸውን መግለጻቸው ይታወቃል።
በ39ሺህ 723 የምርጫ ጣቢያዎች ታዛቢዎች እስካሁን ድረስ ተገኝተው መታዘባቸውን የተናገሩት የቦርዱ ሰብሳቢ፣ የፖለቲካ
ፓርቲዎች እና የግል ተመራጮች ያቀርቧቸው ወኪሎች በ41 ሺህ 798 የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ተገኝተዋል ብለዋል።
ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው መራጮች በመላ አገሪቱ ወጥተው ድምጻቸውን እየሰጡ መሆኑን የገለጹት ሜላት ወርቅ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው መራጮች ሰልፍ
ላይ የቆዩባቸው የምርጫ ጣቢያዎች እና በሌሎች ክልሎች ማጋጠሙን ተናግረዋል።
ይህ የተከሰተው በተለይ የዲጂታል ምዝገባ በተካሄደባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ረዥም የሆኑ ሰልፎች በአዲስ አበባ እና በሌሎች
አካባቢዎች መታየታቸው ተገልጿል።
ይህ የታየው በዲጂታል ወይም በራሳቸው በሞባይል ወይም በድረገጽ የተመዘገቡ መራጮች ላይ መሆኑን ያመለከቱት ሰብሳቢዋ፣ የተፈጠረውን
ሰልፍ ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።
ከ350 ሺህ በላይ ምርጫ አስፈጻሚዎች በመላ አገሪቱ ተሰማርተው እንደሚገኙ ገልጸው፣ በቤንሻንጉል ክልል በዘልማም
እና ሰልዳ የምርጫ ክልሎች በኔትወርክ ችግር የስልክ ግንኙነት የተቸገርንባቸው መረጃ በወቅቱ ለማግኘት አልቻልንም ብለዋል።
በእነሞር እና ኤነር አንድ የምርጫ ክልል የምርጫ ክልል አስፋጻሚ ባልደረባ የክትትል ሥራ ለመሥራት በሞተር ሳይክል ሲሄድ
በደረሰበት አደጋ ሕይወቱ ማለፉን ተናግረዋል።